top of page

ሐምሌ 20፣ 2016 - ''ኢትዮጵያ ካላት አቅም አኳያ ሲታይ ገቢ የመሰብሰብ አቅም እየቀነሰ መጥቷል''

  • sheger1021fm
  • Jul 27, 2024
  • 1 min read

በየዓመቱ መንግስት የሚሰበስበው የግብር መጠን እየጨመረ መጥቷል፡፡


በተጠናቀቀው 2016በጀት ዓመት 466 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስቴር መናገሩ ይታወሳል፡፡


በየዓመቱም የገቢ አሰባሰቡ እየጨመረ መምጣቱን አሃዛዊ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡


ይሁን እንጂ ሀገሪቱ ካላት አቅም አኳያ ሲታይ ገቢ የመሰብሰብ አቅም እየቀነሰ መምጣቱን ጥናት አሳይቷል፡፡


ከሀገሪቱ ጥቅል ሀገራዊ ምርት ከፍተኛ ግብር የተሰበሰበው ከስምንት ዓመታት በፊት ሲሆን እሱም 14 በመቶ ነበር ፣ አሁን ግን ያለው ምጣኔ ከ10 በመቶ በታች መሆኑን ጥናቱ ያሳያል፡፡



ያሬድ እንዳሻው


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page