top of page

ሐምሌ 2፣ 2016 - ጠ/ይ ሚ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ጠዋት ፖርት ሱዳን መግባታቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Jul 9, 2024
  • 1 min read

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚያ ሲደርሱም የሱዳን ጦር አዛዥ ጀነራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን አቀባበል እንዳደረጉላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ተናግሯል፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደ ፖርት ሱዳን የተጓዙት ለሱዳን መረጋጋት የሚያከናውኑት ጥረት ቀጣይ እርምጃ ነው ሲል ፅ/ቤታቸው አስረድቷል፡፡


በሱዳን በጀነራል አብድልፈታህ አልቡርሃን የሚመራው የሀገሪቱ ጦር እና አርኤስኤፍ(RSF) ከተሰኘው ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ጋር ጦርነት ማካሄድ ከጀመሩ ዓመት ከ3 ወራት ሊሆናቸው ነው፡፡

ጦርነቱ ለማስቆም አንዴ በሳውዲ አረቢያ፣ ሌላ ጊዜ በግብፅ ንግግር ለማድረግ ቢሞከርም ዘላቂ መፍትሄ እስካሁን አልመጣም፡፡


ጦርነት በተለይ በዋና ከተማዋ ካርቱም በርትቶ መቀጠሉ ይነገራል፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሄዱትም በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል ወደምትገኘው እና የሀገሪቱ 90 በመቶ ገቢ እና ወጪ ንግድ ወደሚቀለጣጠፍባት ፖርት ሱዳን ከተማ መሆኑ ተነግሯል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page