top of page

ሐምሌ 19፣ 2016 - የአስተዳደር በደል አድርሰዋል የሚል አቤቱታ በህዝቡ ቀርቦባቸው ለማስተካከል ፈቃደኛ ባልሆኑ 46 የመንግስት ተቋማት ላይ ክስ ተመሰረተ

  • Jul 26, 2024
  • 1 min read

የአስተዳደር በደል አድርሰዋል የሚል አቤቱታ በህዝቡ ቀርቦባቸው ለማስተካከል ፈቃደኛ ባልሆኑ 46 የመንግስት ተቋማት ላይ ክስ ተመሰረተ፡፡


የሚፈፀሙ የአስተዳደር በደሎችን መርምሮ እልባት እንዲያገኙና አቤት ባዮችም እምባቸው እንዲታበስ እያደረግኩ ነው የሚለው የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም፤ የደረሱኝን አቤቱታዎች መርምሬ መፍትሄ እንዲያገኙ ከሰጠሁዋቸው በርካታ የመንግስት ተቋማት 46ቱ ያጠፉትን አስተካክሉ የሚል ምክረ ሃሳብ ብሰጥም ዳተኛ ሆነው በመገኘታቸው ለመክሰስ ተገድጃለሁ፡፡


ወደ ፍርድ ቤት ከሄዱት 46 ጉዳዮች 12ቱ ውሳሄ እንዳገኙ፤2ቱ በቅርቡ ውሳኔ ያገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ቀሪዎቹ በሂደት ላይ እንዳሉ የነገሩን በኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተወካይ እምባ ጠባቂ የሆኑት አቶ ደነቀ ሻንቆ፤ የተቋማቱን ማንነት ግን ከመናገር ተቆጥበዋል፤ምንነታቸውን ሁሉም ጉዳዮች በፍርድ ቤት ውሳኔ ካገኙ በኋላ ይፋ እናደርጋለን ብለዋል፡፡



Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡

ሐምሌ 15 2018 በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት የህፃናት ማቆያዎቹ ጥቂት ነበሩ ያለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አሁን ላይ ከፍተኛ መሻሻሎች ታይተውበታል ብሏል፡፡ ጥናቱም በግል እና በመንግስት ማ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page