top of page

ሐምሌ 19፣2015 - ለአፍሪካ የምጣኔ ሐብት ችግሮች በአፍሪካዊያን የተዘየዱ መላዎች ያሻሉ ተባለ

  • sheger1021fm
  • Jul 26, 2023
  • 1 min read

ይህ የተባለው በዛሬው እለት “መረጃ ለውሳኔ ሰጭነት” በሚል መሪ ቃል አህጉር አቀፍ ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄድ በጀመረበት ወቅት ነው፡፡


ጉባኤው ከዛሬ እስከ አርብ ድረስ የሚቆይ ሲሆን የተለያዩ የምርምር እና የጥናት ተቋማት እየተሳተፉበት ነው፡፡


የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር ዳይሬክተር ዶ/ር አምዲሳ ተሾመ እንዲህ ያሉ ጉባኤዎች በኢትዮጵያ መካሄዳቸው የመንግስት ውሳኔ ሰጭ ተቋማት ለሚከውኗቸው ተግባራት በቂ መረጃና ማስረጃ እንዲኖራቸው ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡


ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ የመንግስት የተለያዩ የውሳኔ ሰጪ ተቋማት የሚወስኗቸው ውሳኔዎች ጥናት ላይ የተመረኮዙ ባለመሆናቸው የሚበዙት ስኬታማ ሳይሆኑ ይቀራሉ፤ የተሰሩ ጥናቶችንም ወደ ተግባር ለማውረድ ክስተቶች ይስተዋላሉ ተብሏል፡፡


የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የመንግስት አስፈፃሚ አካላት ውሳኔ ላይ ለመድረስ ወይንም ለሚከወኑት ስራ በመረጃ የተደገፉ አይደሉም ብለዋል፡፡


የሚበዙት ተቋማት በድንገት በኮሚቴዎቹ ውይይት ካደረጉባቸው በኋላ ነው ውሳኔ ላይ የሚደርሱት ይህ በመሆኑም በቂ መረጃ ባለመኖሩ ስኬታማ አይደሉም ማለታቸውን ሰምተናል፡፡



ያሬድ እንዳሻው




 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page