top of page

ሐምሌ 18፣ 2016 - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመስከረም 20፣2017 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ኤርትራ መብረር አንደማይችል እንደተናገረው አሳወቀ፡፡

  • sheger1021fm
  • Jul 25, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመስከረም 20፣2017 ዓ/ም ጀምሮ ወደ ኤርትራ መብረር አንደማይችል ከኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን በደብዳቤ አንደተናገረው አሳወቀ፡፡


ደብዳቤው የተጻፈልኝ ሐምሌ 14፣2016 ዓ.ም ነው ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በራረው ይቋረጣል የተባለበት ምክንያት ግን አልተገለጸልኝም ብሏል፡፡


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ማብራሪያ እየፈለገ መሆኑን ተናግሮ ማንኛውንም ችግር በሰላማዊ መንገድ እና በፍጥነት ለመፍታት ቁርጠኛ ነኝ ሲል ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።


የኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኞች ከመስከረም 20፣2017 ጀምሮ ወደ ኤርትራ የሚደርጉትን በረራ አንደሚያግድ የተናገረው የተጓዦች ሻንጣ ይሰራቃል፣ተደጋጋሚ የበረራዎች እና የሻንጣዎች መዘግየት ያገጥማል በሚል ምክንያት አንደሆነ ተዘግቧል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page