top of page

ሐምሌ 18፣ 2016 - የባህር ማዶ ወሬዎች

  • Jul 25, 2024
  • 2 min read

የኬንያው ፕሬዘዳንት ዊሊያም ሩቶ ከተቃዋሚው የፖለቲካ ጥምረት ወገን የሆኑ አራት ሚኒስትሮችን በአዲሱ ካቢኔ ውስጥ ማካተታቸው ተሰማ፡፡


ለተቃዋሚ ፖለቲከኞቹ ተሰጥተዋል ከተባሉ የሚኒስትርነት ቦታዎች የገንዘብ እና የኢነርጂ ቁልፍ ሹመቶች እንደሚገኙበት ቢቢሲ ፅፏል፡፡


ፕሬዘዳንት ሩቶ ተቃዋሚዎቹን በአዲሱ ካቢኔ ውስጥ ያካተቱት በአገሪቱ መንግስት ላይ ተቃውሞ ባላባራባት አጋጣሚ ነው ተብሏል፡፡


ሩቶ ቀደም ሲል የ11 ሚኒስትሮችን ዝርዝር እወቁልኝ ያሉ ሲሆን ትናንት ደግሞ አራቱን የተቃዋሚ ወገኖች ጨምሮ የ10 የካቢኔ አባላትን እወቁልኝ ማለታቸው ተጠቅሷል፡፡


አራቱ ተሿሚዎች ከዋነኛው የተቃውሞ ጥምረት መሪ ራይላ ኦዲንጋ ጋር ቅርበት ያላቸው እንደሆኑ ቢቢሲ ፅፏል፡፡


የሁሉም ሚኒስትሮች ሹመት ተቀባይት የሚያገኘው ፓርላማው ይሁንታውን ሲሰጥ ነው ተብሏል፡፡


15 ዓመታት በኋላ ረሃብን ከምድር ገፅ ለማጥፋት የተያዘው ውጥን እንደማይሳካ የተባበሩት መንግስታት ሪፖርት አሳየ፡፡


ከመንፈቅ በፊት በተጠናቀቀው አመት የዓለማችን ረሃብተኞች ብዛት 733 ሚሊዮን እንደደረሰ በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡


ከዚህ ጊዜ ከ4 አመታት በፊት ከነበረው ሲመሳከርም የረሃብተኞቹ ብዛት በ152 ሚሊዮን ያህል ጨምሯል ተብሏል፡፡

እንደ ሪፖርቱ ከአለማችን ከእያንዳንዳቸው 11 ሰዎች አንዱ ረሃብተኛ ነው፡፡


በአፍሪካ ደግሞ ችግሩ የባሰ እንደሆነ በሪፖርቱ መጠቀሱን አልጀዚራ ፅፏል፡፡


በአፍሪካ ከአምስት ሰዎች መካከል አንዱ ረሃብተኛ እንደሆነ ሪፖርቱ አሳይቷል፡፡


በዚህ አዝማሚያ ከ15 አመታት በኋላ ረሃብን ከምድረ ገፅ የማጥፋቱ ውጥን ላም አለኝ በሰማይ ዓይነት ነው ተብሏል፡፡


ጦርነት ፣ የአየር ለውጥ እና የኢኮኖሚ ቀውስ በረሃብ አባባሽነት ተጠቅሰዋል፡፡



የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ የአሜሪካን እንደራሴዎች ጦር ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩላቸው ጠየቁ፡፡


ኔታንያሁ ለኮንግረስ አባላቱ የጋራ ስብሰባ ንግግር ማድረጋቸውን ቢቢሲ ፅፏል፡፡


ኔታንያሁ በዚሁ ንግግራቸው ጠላቶቻችን ጠላቶቻችሁ ናቸው ድላችንም ድላችሁ ነው ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ለኮንግረሱ ባደረጉት ንግግር ኢራንን በጠላትነት አጉልተው ማቅረባቸው ታውቋል፡፡


ኔታንያሁ ለአሜሪካ እንደራሴዎች ንግግር ያደረጉት የጋዛው ጦርነት ባስከተለው ከፍተኛ ውድመት እና እልቂት የተነሳ የሀሳብ ክፍፍሉ እየበረታ በመጣበት ወቅት ነው ተብሏል፡፡


ከኮንግረሱ መምከሪያ ውጭ በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ጦርነት አውጋዦች ኔታንያሁን በጦር ወንጀለኝነት በመኮነን ድምፃቸውን አጉልተው መኮነናቸው ተሰምቷል፡፡


ወደ አዳራሹ በመዝለቅ ንግግራቸውን ለማወክ ከሞከሩት መካከል 5ቱ ተይዘው መታሰራቸው ተሰምቷል፡፡


በኔታንያሁ ንግግር ወቅት በአዳራሹ ያልተገኙ ዴሞክራት እንደራሴዎች ነበሩ ተብሏል፡፡


በጋዛው ጦርነት የአሜሪካ መንግስት ለእስራኤል ታላቅ የፖለቲካ ፣ የጦር እና የዲፕሎማቲክ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱ ይነገራል፡፡


የኔነህ ከበደ

Recent Posts

See All
የሐምሌ 15 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሞሪታንያ በሞሪታንያ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ በደረሰ የባህር አደጋ 144 ጥገኝነት ፈላጊዎቹ ሳይሞቱ አልቀረም ተባለ፡፡ የአደጋው ሟቾች መነሻዋን ከጋምቢያ በማድረግ ወደ ስፔን በማምራት ላይ በነበረች ጀልባ የተሳፈሩ ጥገኝነት ፈላጊዎች እንደሆኑ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ በጀልባዋ ተሳፍረው የነበሩት በሙሉ ከተለያዩ የአፍ

 
 
 
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡

ሐምሌ 15 2018 በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት የህፃናት ማቆያዎቹ ጥቂት ነበሩ ያለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አሁን ላይ ከፍተኛ መሻሻሎች ታይተውበታል ብሏል፡፡ ጥናቱም በግል እና በመንግስት ማ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page