top of page

ሐምሌ 18፣2015 - ባለፈው መንፈቅ ብቻ በአትላንቲክ የውቅያኖስ መስመር ከ800 የማያንሱ ስደተኞች ሕይወት ጠፍቷል ተብሏል

  • Jul 25, 2023
  • 1 min read

በምዕራብ አፍሪካዊቱ አገር ሴኔጋል የጀልባ ተገልብጦ መስጠም አደጋ የገጠማቸው የ17 ሰዎች አስከሬን ተገኘ፡፡


አደጋው የገጠማቸው ስደተኞች ሳይሆኑ እንዳልቀረ መገመቱን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡


2 ሰዎችን በሕይወት ማትረፍ እንደተቻለ ታውቋል፡፡


ጀልባዋ ምን ያህል ሰዎችን አሳፍራ እንደነበር ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም ተብሏል፡፡


በአትላንቲክ ውቅያኖስ የሚደረግ የስደተኞች የጀልባ ጉዞ አደጋ እየተደገገመበት መምጣቱ ይነገራል፡፡


ከጥቂት ሳምንታት በፊት ከ300 በላይ ስደተኞችን አሳፍራ ከሴኔጋል የተነሳች ጀልባ የት እንደገባች መጥፋቱን ዘገባው አስታውሷል፡፡


ባለፈው መንፈቅ ብቻ በዚሁ የውቅያኖስ መስመር ከ800 የማያንሱ ስደተኞች ሕይወት ጠፍቷል ተብሏል፡፡


የነኔነሀህ ከበደ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz



Recent Posts

See All
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 
የነሐሴ 6 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ደቡብ_አፍሪካ በደቡብ አፍሪካ በአንድ የማዕድን ዝቃጭ ማስወገጃ ስፍራ መደርመስ 14 ሰዎች የሞቱበት አደጋ እየተመረመረ ነው ተባለ፡፡ ሌሎች 8 ሰዎች ደግሞ አካላዊ ጉዳት እንደገጠማቸው ቢቢሲ ፅፏል፡፡፡ በዝቃጩ ውስጥ የተቀበሩ ሌሎች ሰዎች ሳይኖሩ አይቀሩም ተብሏል፡፡ በአደጋው የሞቱት እና አካላዊ ጉዳት የገጠማቸው ሕ

 
 
 
የነሐሴ 5 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#አሜሪካ የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በጦርነቱ ለተገደሉብን ወታደሮቻችን ካሣ ልትከፍል ይገባል አሉ፡፡ ቀደም ሲል በጦርነቱ አሜሪካ ላደረሰችባት ጉዳት ሁሉ ካሣ እንዲከፈላት የጠየቀችው ኢራን እንደነበረች አልጀዚራ አስታውሷል፡፡ ትራምፕ የተገደሉባቸው የጦር ባልደረቦች ብዛት ባይጠቅሱም እኛም ለተገደሉብን

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page