top of page

ሐምሌ 17፣2016 - የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የስርዓተ ፆታ ፖሊሲ ሊኖራቸው እንደሚገባ ተጠቆመ

  • sheger1021fm
  • Jul 24, 2024
  • 1 min read

የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የስርዓተ ፆታ ፖሊሲ ሊኖራቸው እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡


በኢትዮጵያ ያሉ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የስርዓተ ፆታን ሚዛን የሚያስጠብቁበት ምንም አይነት ፖሊሲ እንደሌላቸው ፎጆ ሚዲያ ኢንስቲትዩት የተባለ አለም አቀፍ ተቋም ተናግሯል፡፡ተቋሙ ሴት የሚዲያ ባለሙያዎች በየተቋማቸው የሚደርሱባቸውን ችግሮች ሊያጠና መሆኑን ጠቁሟል፡፡


ጥናቱ ችግሮቱን በመለየት መፍትሄዎቹን እንደሚያመላክትና የጥናቱ ግብም ሁሉም የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የስርዓተ ፆታ ፖሊሲ እንዲኖራቸው ማስቻል መሆኑን ለጥናቱ ግብዓት ለማሰባሰብ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ያገኘናቸው በፎጆ ሚዲያ ኢንስቲትዩት የኢትዮጵያ አስተባባሪ የሆኑት ኢልሃም አሊ ነግረውናል፡፡


እንደ አስተባባሪዋ አነጋገር በኢትዮጵያ በአብዛኛው ሴት ጋዜጠኞች ከወንዶች የሙያ አጋሮቻቸው አንፃር በደሞዝ ክፍያ የማነስ፣ተመጣጣኝ የስራ እድገት ያለማግኘት፣ የስራ ቦታ ላይ ፆታዊ ጥቃትና ሌሎችም ይደርስባቸዋል፤ጥናቱ ለእነዚህ ችግሮች መፍትሄዎችን ይዞ የሚመጣ ነው ብለዋል፡



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page