top of page

ሐምሌ 17፣2016 - በኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የግል ድርጅት ሃላፊዎች እንዲሁም ጋዜጠኞች የሙስና ተሳተፊዎች መሆናቸውን ጥናት አሳየ

  • sheger1021fm
  • Jul 24, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የግል ድርጅት ሃላፊዎች እንዲሁም ጋዜጠኞች የሙስና ተሳተፊዎች መሆናቸውን ጥናት አሳየ፡፡


ጥናቱ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር 21ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ የቀረብ ነው፡፡


በኢትዮጵያ ሊታመኑ የሚገባቸው አካላት የሙስና ተሳታፊ መሆናቸው በጥናቱ ተለይቷል፡፡


መታመን የነበረባቸው የመንግስትን እና የማህበረሰብን ሃላፊነት የያዙ አካላት ቀጥተኛ የሙስና ተሳትፎ እንዳላቸው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር ያስጠናው ጥናት አሳይቷል፡፡


ጥናቱን ያቀረቡት በማህበሩ ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት አረጋ ሹመቴ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ሙስና ካለባቸዉ አገራት ተርታ እንደምተገኝ አስረድተዋል፡፡


ጥናት አቅራቢዉ በሙስና ወንጀል ከፍተኝ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች የወረዳ እና የቀበሌ አመራሮች አገልግሎት የሚሰጡ የመንግስት መስሪያ ቤት የሚሰሩ ወይንም ሲቪል ሰርቫንት ተሳታፊዎች ናቸዉ ሲል ጠቁሟል፡፡


የንግድ ድርጅቶችን የሚመሩ የሰራ ሃላፊዎችም በሀገሪቱ ያለዉን የአሰራር ወጣ ወረድ አልያም ቢሮከራሲ በቀላሉ ለማለፍ በሚል የሙስና ተሳታፊዎች ናቸው ተብሏል፡፡


እነዚህ ሁሉ አካላት የሙስና ተሳታፊ የሆኑት ደግሞ ተቋማዊ አሰራር እየተፍረከረከ በመምጣቱ እና ሰራተኛው ለኑሮ የሚበቃ ገቢ ባለመኖሩ እንደሆነ ጥናት አቅራቢው ነግረውናል፡፡


ያሬድ እንዳሻው



Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page