top of page

ሐምሌ 15፣ 2016 - ከ21 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን በዚህ ወቅት እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያሳያል

ከ21 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያዊያን በዚህ ወቅት እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡


ያም ሆኖ እርዳታ አቅራቢ ድርጅቶች በተለያዩ አካባቢዎች ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት፤ በቂ እንዳልሆነ የሚነገርለትን እርዳታ እንኳን በአግባቡ ማደረስ አልቻሉም፡፡


በግጭቶች እና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት ለእርዳታ ፈላጊነት ለተዳሩጉት፤ ለእነዚህ ሰዎች ድጋፍ እንዲደረግላቸው በተገደጋጋሚ ጥሪ ሲቀርብ ይሰማል፡፡


በሌላ በኩል የተሰበሰቡ እርዳታዎችም በትክክል ለተረጂዎች ይደርሳሉ ወይ የሚለው በብዙዎች ጥያቄ የሚነሳበት ነው፡፡


እርዳታዎቹ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች በተገቢው ተደራሽ እንዲሆን እና በሰላም ዙሪያ የሚሰሩ ስራዎችም ውጤታማ የመሆን እድላቸው ሰፊ የሚሆነው፤ ረጂ አካላት ሰንሰለት ሳያበዙ በቀጥታ ተረጂዎችን አግኝተው ማገዝ ሲችሉ እንደሆነ ይታመናል፡፡


በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ህዝብን እናግዛለን፣ እንደግፋለን ብለው የተመዘገቡ ድርጅቶች ቁጥርም ከ5,000 በላይ እንደሆኑ ተነግሯል፡፡


ለመሆኑ እነዚህ ረጂ አካላት ድጋፍም ሆነ ሌሎች በሰላም ዙሪያ ያሏቸውን የመፍትሄ ሀሳቦቻቸውን ይዘው ወደ ተጎጂዎች ድረስ ወርደው ለመስራት፤ አስቻይ ሁኔታ በሀገሪቱ አለ ወይ ስንል ሀገር በቀልና የውጭ ረጂ ተቋማት እንዲሁም የሚመለከተው አካልን ጠይቀናል፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን ያሰናዳውን በፍቅሩ አምባቸው



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page