top of page

ሐምሌ 14 2017 - ደረጃ ሳያሟሉ ለገበያ ቀርበው የነበሩ የተለያዩ ምርቶች በክትትል እንዲወገዱ መደረጋቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚ/ር ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Jul 21
  • 1 min read

Updated: Jul 22

የለስላሳ መጠጦች እና የጃር ውሃን ጨምሮ የተቀመጠውን ደረጃ ሳያሟሉ ለገበያ ቀርበው የነበሩ የተለያዩ ምርቶች በክትትል እንዲወገዱ መደረጋቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ተናገረ።


ምርቶቹን ለገበያ ባቀረቡት ነጋዴዎች ላይ ፍቃዳቸውን ከማገድ በወንጀል እስኪጠየቁ የደረሰ እርምጃ ተወስዷልም ብሏል።


የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በሀገር ውስጥ የተመረቱ እና ከውጪ የገቡ የተለያዩ ምርቶች የተቀመጠውን አስገዳጅ ደረጃ ስለሟሟላታቸው ለማረጋገጥ፤ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመትም ባለሞያዎችን በገበያዎች በማሰማራት ቁጥጥር ማድረጉን ጠቅሷል።

ree

በቁጥጥር ስራውም ከተቀመጠው ደረጃ በታች የሆኑ የተለያዩ ምርቶች መገኘታቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ድኤታ አቶ እንዳለው መኮንን ነግረው ነግርውናል።


የአርማታ ብረት፣ የልብስ ሣሙና፣ የለስላሣ መጠጦች እና የጃር ውሃ የተቀመጠውን ደረጃ ሳያሟሉ ወደ ገበያ ተሰራጭተው ካገኘናቸው ምርቶች መካከል ናቸው ብለዋል።


ምርቶቹን ለገበያ ባቀረቡት ነጋዴዎች ላይ ፍቃዳቸውን ከማገድ በወንጀል እስኪጠየቁ የደረሰ እርምጃ ተወስዷልም ብለዋል ሚኒስትር ድኤታው።


ህብረተሰቡ ከደረጃ በታች ስለሆኑት እነዚህ ምርቶች አውቆ በመግዛት ከመጠቀም እንዲቆጠብ ለማስገንዘብ ደግሞ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እናስነግራለን ብለዋል አቶ እንዳለው።


የተቀመጠውን አስገዳጅ ደረጃ አላሟላም የተባለ እና እያንዳንዱ 1,200 ኪሎ ግራም የሚመዝን 8,84 ጥቅል የአርማታ ብረትም በዓመቱ ለገበያ እንዳይቀርብ ተደርጓል ተብሏል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/567u56/


ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page