top of page

ሐምሌ 13፣ 2016 - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ6ተኛ ክፍል ውጤት ይፋ አደረገ፡፡

  • sheger1021fm
  • Jul 20, 2024
  • 1 min read

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ6ተኛ ክፍል ውጤት ይፋ አደረገ፡፡


ቢሮው የ2016 የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና የማለፊያ ነጥብ 50 ከመቶ እንዲሆን ተወስኗል ብሏል፡፡


ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ደግሞ 45 ከመቶ እንዲሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት ወስኗል፡፡


በ2016 የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 85ሺ 46 በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች በቀን እና በማታ ትምህርታቸውን ከተከታተሉ ተማሪዎች መካከል 94 ነጥብ 3 የሚሆኑ ተማሪዎች 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ አምጥተዋል፡፡


ቀሪ 5 ነጥብ 7 ከመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ማለፊያ ነጥብ አላመጡም ሲል ትምህርት ቢሮው ባወጣው መረጃ ተመልክተናል፡፡


በረከት አካሉ


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page