ሐምሌ 13፣ 2016 - በእርስ፣ በእርስ ግጭት የሚዳከመው የሀገር ኢኮኖሚ
- sheger1021fm
- Jul 20, 2024
- 1 min read
በተለያዩ አካባቢዎች ያለው የእርስ በእርስ ግጭት ማባሪያ አላገኘም፡፡
ችግሮችን በሰላም እንፍታ የሚሉ ድምጾች ቢሰሙም ተግባራዊ እርምጃ ግን እየታየ አለመሆኑ ግምቱ ሊቀጥል እንደሚችል ጠቋሚ ነው፡፡
ቀጣይነት ያለው የእርስ በእርስ ግጭት ደግሞ በሂደት የሌሎችን ሃገራትና ቡድኖች ጣልቃ ገብነት እያስከተለ ሌሎች የራሳቸውን ጥቅም የሚያስጠብቁበት ወደ መሆን ይሸጋገራል፡፡
እና ውጤቱም አስከፊ ሊሆን ይችላል ሲሉ ሸገር ያነጋገራቸው የፖለቲካ ሳይንስ መምህር አሳስበዋል፡፡
በግጭቱ ምክንያት ምጣኔ ሀብቱም በእጅጉ እየተጎዳ መሆኑን ጥናቶች ያሳዩ ሲሆን ግጭቱ በዚሁ ከቀጠለ የሃገርን ህልውናም ሊፈትን ይችላል ተብሏል፡፡
ያሬድ እንዳሻው
Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw
Comments