top of page

ሐምሌ 13፣ 2016 - የሴት ልጅ ግርዛት እና ያለ እድሜ ጋብቻ የመሳሰሉ ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶች በሴቶች በቤተሰብ ከፍ ሲልም እንደ ሃገር በብዙ የሚሰሙ መሆናቸው ይታወቃል

  • Jul 20, 2024
  • 1 min read

Updated: Jul 24, 2024

የሴት ልጅ ግርዛት እና ያለ እድሜ ጋብቻ የመሳሰሉ ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶች በሴቶች በቤተሰብ ከፍ ሲልም እንደ ሃገር በብዙ የሚሰሙ መሆናቸው ይታወቃል፡፡


በአለም አቀፍ ደረጃም የሰብአዊ መብት ጥሰት ሆኖ የተፈረጀው የሴት ልጅ ግርዛት በኢትዮጵያም በተለይ ቀድሞ ባለው ጊዜ መኖሩ ታውቆ ልማዱ እንዲቀር ብዙ ሲባል ቆይቷል፡፡


እ.ኤ.አ 2016 እስከ 99 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች የተገረዙበት የሶማሌ ክልል ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ በቅደም ተከተል ከ91 በመቶ እስከ 73 በመቶ ሴቶችን በመግረዝ አፋር ፣ ሀረሪ ፣ ኦሮሚያ እና ጋምቤላ ክልሎች ከሁለት እስከ 5ተኛ ደረጃ ይይዛል፡፡


አዲስ አበባ ከተማም 54 በመቶ ሴቶች የተገረዙባት መሆኗን ከስምንት አመት በፊት የተጠና ጥናት ያሳየ ሲሆን እንደ አጠቃላይ ደግሞ በኢትዮጵያ የሴቶች ግርዛት 65 በመቶ ያለ እድሜ ጋብቻ ደግሞ 58 ከመቶ መሆኑን ከሴቶችና ማሀበራዊ ጉዳይ ሚንስትር ያገኘው መረጃ ያሳያል፡፡


በዚህም ምክንያት በፈረንጆቹ 2025 የሴት ልጅ ግርዛት እና ያለድሜ ጋብቻን ታሪክ አደርጋለሁ ብላ ስትሰራ የቆየችው ኢትዮጵያ ተሳክቶላት ይሆን ወይ ስንል የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ጠይቀናል፡፡



Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page