top of page

ሐምሌ 12፣2015 ኢትዮ ቴሌኮም በውድድር ገበያው በዘንድሮ በጀት ዓመት ካሰብኩት በላይ አሳክቻለሁ አለ።

  • Jul 19, 2023
  • 1 min read

የፋይናንስ አካታችነትን ለማስጓዝ ወደ ሥራ የገባው ቴሌ ብር እስካሁን በኢኮኖሚ ውስጥ 679.2 ቢሊየን ብር መላወሱን የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ተናግረዋል።


ኩባንያው በዘንድሮ በጀት ዓመት በገቢ ደረጃ የእቅዴን 101% አሳክቻለሁ ብሏል።


75.8 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ሰምተናል።


ከአለምአቀፍ ኢንተርኮኔክት ሮሚንግ፣ ከመሠረተ ልማት ኪራይና ከሐዋላ አገልግሎት 164.1 ሚሊየን ዶላር በበጀት ዓመቱ ተገኝቷል ብሏል።


4.23 ቢሊየን ብር ወይም 78.4 ሚሊየን ዶላር ለብድር ተከፍሏል።


ኢትዮ ቴሌኮም በዘንድሮ በጀት ዓመት 20.8 ቢሊየን ብር ግብር መክፈሉን ተናግሯል።


የደንበኛ ቁጥር 72 ሚሊየን ደርሷል መባሉን ሰምተናል።


ይህ ውጤት በውድድር ገበያ ደንበኞችን ለማቆየት በተሠራው ሥራ የመጣ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል።


ኩባንያው አገልግሎት ተቋርጦባቸው የነበሩ አካባቢዎችን በተቻለው ፍጥነት ማስጀመሩን ዛሬ የዓመቱን አፈፃፀም በተናገረበት ግዜ ተናግራል።



ተህቦ ንጉሴ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz


Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ።

ነሐሴ 7 2018 በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ። ከአስር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የታየው የኤልኒኖ ተፅዕኖ የእህል ምርት ውጤትን ከ15 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎ እንደነበር አንድ የዘርፉ ተመራማሪ ነ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page