ሐምሌ 11 2017 - ለተቀጣሪ ሠራተኞች ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲኖር ማድረግ እንደ አንድ የሰብዓዊ መብት ጉዳይ እየታየ ነው ተባለ
- sheger1021fm
- Jul 18
- 1 min read
ከኢትዮጵያ ምርቶችን የሚገዙ የአውሮፓ ሀገራት እና አሜሪካ ጉዳዩን እንደ አንድ ቅድመ ሁኔታ እያቀረቡት እንደሆነ ተጠቅሷል።
ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል በኢትዮጵያ በህግ እንዲወሰን ካልተደረገ እነዚህ ሀገራት ምርቶችን ከኢትዮጵያ መግዛት ሊያቆሙ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሞያዎች ማህበር ባዘጋጀው አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ ሲነገር ሠምተናል።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሞያዎች ማህበር ዛሬ ሲኤምሲ በሚገኘው መስሪያ ቤቱ ማካሄድ የጀመረው አለም አቀፍ ጉባኤ እስከ ነገ ይቆያል።

በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዙሪያ የተዘጋጁ የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበውም ተሳታፊዎች እየተወያዩባቸው ነው።
ማህበሩ እንዲህ አይነቱን አለም አቀፍ ኮንፈረንስ ሲያዘጋጅ የዘንድሮው ለ22ኛ ጊዜ እንደሆነ ሠምተናል።
ከ34 ዓመት በፊት የተመሠረተው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ባለሞያዎች ማህበር አሁን ከስድስት ሺህ በላይ አባላት አሉኝ ብሏል።
ንጋቱ ረጋሣ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments