top of page

ሐምሌ 11፣ 2016 - የአፋርና የሶማሌ ክልሎች፤ ግጭት ለማቆም መስማማታቸውን ተናገሩ

በአፋርና በሶማሌ ክልል መካከል እያሰለሰ የሚፈጠር ግጭት ለንጹሃን ሞትና መፈናቀል ምክንያትት ሆኖ የዘለቀውን ለማቆም ሁለቱ ክልሎች መስማማታቸው ተናግረዋል፡፡


በይዞት ይገባኛል ጥያቄ ምክንያት በተደጋጋሚ ግጭት ከሚነሳባቸው ግጭቶች መካከል የአፋርና የሶማሌ ክልሎች ይገኙበታል፡፡


ክልሎቹ ዛሬ በብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት መግለጫ ተኩስ ለማቆም መስማማታቸው ተናግረዋል፡፡


የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር አወል አርባ ‘’ግጭት ለማቆም ተስማምተናል’’ ብለዋል፡፡

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሙስጠፌ መሀመድ በበኩላቸው በሁለቱ ክልሎች መካከል ለንጹሃን ሞትና መፈናቀል ምክንያት የሆነው ግጭት ለማቆም ‘’በፌዴራል ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች በተሰጠው ውሳኔ ከስምምነት ተደርሷል’’ ብለዋል፡፡


ሙስጠፌ መሐመድ ባለፉት ዓመታት ጀምሮ የነበረው ግጭት ለሰው ሕይወት መጥፋትና ላላስፈላጊ ውድመት ምክንያት ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡


አሁን ግን ይህን ግጭት ለመፍታት ሁለቱ ክልሎች መስማማታቸውን ተናግረዋል፡፡


በስምምነቱ መሰረትም ግጭቶች እንዲቆሙና የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ ከስምምነት ተደርሷል ብለዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page