top of page

ሐምሌ 11፣ 2016 - የሆልቲካልቸር ዘርፍ ከአምናው 123 ሚሊን ዶላር ቅናሽ አለው ተብሏል

  • sheger1021fm
  • Jul 18, 2024
  • 1 min read

የሆልቲካልቸር ዘርፍ በዚህ ዓመት ያስገኘው የውጪ ምንዛሪ ገቢ ከአምናው ያነሰ ነው፡፡


ገቢው ከአምናው 123 ሚሊን ዶላር ቅናሽ አለው ተብሏል፡፡


ይህንን ያሉት የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ ናቸው።


ሚኒስትሩ እንዳሉት በዚህ ዓመት የሆልቲ ካልቸር ምርቶች ወደ ውጪ በመላክ 535 ሚሊዮን ዶላር አስገኝቷል ባለፈው ዓመት ግን 658 ሚልየን ዶላር ገቢ ተገኝቶ ነበር።


ዘርፉ ከቡና በመቀጠል ሁለተኛው የውጪ ምንዛሪ አስገኚ ቢሆንም የተለያዩ ችግሮች ይታዩበታል ብለዋል።

ይህንን ለማስተካከል ብሔራዊ የሆልቲካልቸር #ረቂቅ መመሪያ እየተዘጋጀ ነው ተብሏል።


ወደ ውጪ ከሚላከው የሆልቲካልቸር ምርት፤ አበባ በገቢ ቅድሚያ የሚይዝ ሲሆን ከፍራፍሬ የሚገኘው ገቢ ከ100 ሚልየን ዶላር አይበልጥም ተብሏል።


ኢትዮጵያ በዘርፉ ከፍተኛ አቅም ቢኖራትም ለዘርፉ የሚሰጠው የፋይናንስ አቅርቦት አንስተኛ መሆን፤ መሰረተ ልማት አለመሟላት፤ የገበያ መረጃ እጥረት ችግር እንደሆነ ተነግሯል፡፡


ክልሎች ላይ ለአልሚዎች በፍጥነት መሬት አለማስተላለፍ ችግር ይታያልም መባሉን ሰምተናል።



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page