top of page

ሐምሌ 11፣ 2016 - በኢትዮጵያ ከዓመታ በፊት የግሉ ዘርፍ፤ 12 ከመቶ ሰፋፊ እርሻ ያስተዳድር እንደነበረ ቢነገርም አሁን ግን ወደ 1 በመቶ ዝቅ ማለቱን ጥናት አሳይቷል

በኢትዮጵያ ከዓመታ በፊት የግሉ ዘርፍ፤ 12 ከመቶ ሰፋፊ እርሻ ያስተዳድር እንደነበረ ቢነገርም አሁን ግን ወደ 1 በመቶ ዝቅ ማለቱን ጥናት አሳይቷል፡፡


የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከሰት እና በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያለ የሰላም እጦት ለዘርፉ መዳከም ከሚነሱት ቀዳሚ ችግሮች መካከል መሆናቸውን ሰምተናል፡፡


በግብርናው ዘርፍ የተሰማሩ የግል አልሚዎችም ለስራቸው መቀዛቀዝ የሚያነሱት ምክንያት ይህንኑ ነው፡፡


ከቅርብ አመታት ወዲህ እንደሀገር በተፈጠሩብን የሰላም መደፍረስ ችግሮች ምክንያት ዘርፉ የሚጠበቅበትን እየሰራ አይደለም የሚሉት የኢትዮጵያ ሰብል አምራቾች እና ላኪዎች ባለ ብዙ ዘርፍ ማህበር ፕሬዝደንት አቶ መልካሙ አብርሀም በተለያዩ አካባቢዎች ሰፋፊ እርሻዎች ላይ በፀጥታ ችግር የተነሳ ጉዳት መድረሱን ነግረውናል፡፡


በዚህ ምክንያትም በፍጥነት አገግሞ ወደ ስራ ያልተመለሱ እንዳሉ አቶ መልካሙ ይናገራሉ፡፡



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page