top of page

ሐምሌ 11፣2015 - ከአሜሪካ ፔንታገን በስህተት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ መልዕክቶችን ወደ ማሊ መላካቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Jul 18, 2023
  • 1 min read

Updated: Jul 19, 2023

ሐምሌ 11፣2015


ከአሜሪካ መከላከያ መስሪያ ቤት ፔንታገን በስህተት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የኤሌክትሮኒክስ መላ መልዕክቶችን ወደ ማሊ መላካቸው ተሰማ፡፡


በስህተት ከተላኩት የኢ-ሜይል መልዕክቶች ውስጥ ብርቱ ብርቱ ሚስጥሮችም የሚገኙባቸው እንዳሉ ቢቢሲ ፅፏል፡፡


የፔንታጎን ሹሞች ጉዳዩን በመላ እንይዘዋለን ማለታቸው ተሰምቷል፡፡


ይሁንና ዋጋቸው ከፍ ያለ መረጃዎችን የያዙ መልዕክቶች እጅግ ሚስጥራዊ የሚል ፅሁፍ ያልሰፈረባቸው ናቸው ተብሏል፡፡


የማሊ ወታደራዊ መንግስት የሩሲያ ጥብቅ ወዳጅ መሆኑ ይነገራል፡፡


ከአሜሪካ የመከላከያ መስሪያ ቤት በስህተት ያፈተለኩትን ኢ-ሜይሎች ሌሎች ወገኖች ሊያገኟቸው መሞከራቸው እንደማይቀር መገመቱ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡



የኔነህ ከበደ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Commenti


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page