top of page

ሐምሌ 11፣2015 - በበጎ ስራዎቻቸው አርዓያ ናቸው የተባሉ 4 ወጣቶች ምስጋና ተሰጣቸው

በሽማግሌዎች ምርቃት ታጅበው ምስጋናው እና የእውቅና ሰርተፍኬት የተሰጣቸው ማስተር አብነት ከበደ፣ ወንድም ካሊድ፣ ሚኪያስ ለገሰ እና ዘካሪያስ ኪሮስ ናቸው፡፡


ለወጣቶቹ የዕውቅና ፕሮግራም የተሰናዳላቸው በጉለሌ ክፍለ ከተማ ደጋፊነት ኤሴቅ ሁነት አዘጋጅ ባሰናዳው ስነስርዓት ላይ ነው፡፡


እውቅናው ከተሰጣቸው መካከል አንዱ የሆነው ሚኪያስ ለገሰ የተቸገሩ ሰዎች እንዲረዱ እና ህክምና እንዲያገኙ የሚሰራው የሰሊሆም የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል መስራች ነው፡፡


ማስተር አብነት ከበደ በተለይ ደጋፊ፣ ጧሪ የሌላቸውን አረጋዊያንን ከበጎ ፍቃደኞች ገንዘብ በማሰባሰብ ቤት በማደስ፣ ልብስ፣ ምግብ በመስጠት ይታወቃል፡፡


ወንድም ካሊድ፣ የካሊድ ፋውነዴሽን መስራች ሲሆን እሱም በተመሳሳይ ኑሮ ፊቷን ያዞረችባቸውን ሶዎች ያግዛል፡፡


ዘካሪያስ ኪሮስ በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ እማማ ዝናሽ ከሚባሉ አረጋዊት ጋር በሚሰራቸው ቪዲዮዎች የሚታወቅ ሲሆን ደጋፊ ያጡ ሰዎችን በመርዳት ይታወቃል፡፡

በዛሬው የእውቅናና የምስጋና ፕሮግራም ላይ የጉላሌ ክፍለ ከተማ ሃላፊዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተገኝተዋል፡፡



ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Komentar


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page