top of page

ሐምሌ 10፣ 2016 - ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ''ኢትዮጵያ ውስጥ የሽግግር መንግስት’’ አይኖርም ሲሉ የተናገሩት የምክክር ኮሚሽንን እንደማይወክል ይታወቅልኝ አለ

ሐምሌ 10፣ 2016


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በአዲስ አበባ አጀንዳ ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ‘’የሽግግር መንግስት’’ አይኖርም ሲሉ የተናገሩት ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን እንደማይወክል ይታወቅልኝ አለ፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ በወቅቱ በመደረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ‘’የሽግግር መንግስት የሚል ሀሳብ ይነሳል፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከእንግዲህ የሽግግር መንግስት አይኖርም የሚኖረው በምርጫ የተመረጠ መንግስት ብቻ ነው’’ ማለታቸው ይታወሳል፡፡


ይህን ተከትሎም በርካቶች በምክር ሂደቱ የሽግግር መንግስት ይቋቋም የሚል አጀንዳ ቢቀርብ ‘’ተፈጻሚ አይሆንም ይህም መንግስት አጀንዳዎችን የመፈጸም ፍላጎት የለውም ኮሚሽኑም ውጤት ላያመጣ ይችላል’’ የሚል ሃሳብ ሲነሳ ቆይቷል፡፡


ለዚህም ምላሽ የሰጠው የምክክር ኮሚሽን እንዲታወቅልኝ የምፈልገው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ የተናገሩት የመንግስታቸውን እና ፓርቲቸውን ሀሳብ ነው ብሏል፡፡


ኮሚሽኑ ይህን የተናገረው በመጭው ሳምንት በጋምቤላ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፣ ሐረሪ እና በድሬዳዋ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት እንደሚጀምር በተናገረበት ወቅት ነው፡፡


ኮሚሽነር መላኩ ወለደ ማርያም ‘’ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በወቅቱ በመደረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የመንግስታቸውን እና የፓርቲያቸውን አቋም ሊሆን ይችላል ይህ ማለት የእኛን አሰራር የኛን አካሄድ ይገዛል ማለት እንዳል ሆነ በግልጽ መታወቅ አለበት’’ ብለዋል፡፡




ያሬድ እንዳሻው


תגובות


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page