top of page

ሐምሌ 10፣ 2016 - ''በምክክር ሂደቱ በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ አካላት የመሳተፍ ፍላጎት ካላቸው ደንነታቸው ተጠብቆ እንዲሳተፉ የማድረግ አቅሙ አለኝ'' የምክክር ኮሚሽን

  • sheger1021fm
  • Jul 17, 2024
  • 1 min read

በትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ታጣቂዎች በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የመሳተፍ ፍላጎት ካላቸው ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሳተፉ አደርጋለሁ ሲል የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡


ኮሚሽኑ ይህን የተናገረው በክልሎች አጀንዳ ለማሰባሰብ ዝግጅት ማጠናቀቁን ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡


በምክክር ሂደቱ በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ አካላት የመሳተፍ ፍላጎት ካላቸው ደንነታቸው ተጠብቆ እንዲሳተፉ የማድረግ አቅሙ አለኝ ሲል ኮሚሽኑ አስረድቷል፡፡


የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍር አርአያ ከታጣቂዎቹ ይሁንታ እስከተገኘ ድረስ የእነሱ ደህንነት ተጠብቆ በምክክር ሂደቱ እንዲሳተፉ የማድረግ ኮሚሽኑ አቅም አለው ብለዋል፡፡

ree

ግን የእነሱ ይሁንታ ካልተገኘ መንግስትንም ሆነ የሚመለከተውን አካል ለመጠየቅ ኮሚሽኑ ይቸገራል ሲሉ ዋና ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡


የኮሚሽኑ ኮሚሽነር መስፍን አርአያ በመጪው ሳምንት በጋምቤላ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በድሬዳዋና በሐረሪ አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ይጀመራል ብለዋል፡፡


በአፋር ደግሞ አሁን ላይ ከፍተኛ ሙቀት ስላለ በጥቅምት ወር አጀንዳ ማሰባሰብ እንደሚጀመር ኮሚሽነሩ አስረድተዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page