top of page

''ለ40/60 እና ለ20/80 ቤት ገንብቶ ለነዋሪዎቹ ለማድረስ ችግር ገጥሞኛል'' የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

  • sheger1021fm
  • Jun 27, 2024
  • 1 min read

የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ለ40/60 እና ለ20/80 ቤት ገንብቶ ለነዋሪዎቹ ለማድረስ ችግር ገጥሞኛል አለ፡፡


መንግስት አቅሙ ላላቸው መሬት እያቀረበ በማህበር ተደራጅተው ቤት እንዲገነቡ እያደረገ ነው ሲል ኮርፖሬሽኑ ተናግሯል፡፡


ይሁንና ይህ አቅሙ ላላቸው ብቻ እንጂ ሌሎችን ቆጣቢዎች አያካትትም ተብሏል፡፡


በአዲስ አበባ ለረጅም ዓመታት ቤት ለማግኘት የቆጠቡ ነዋሪዎች እኛ ቤት ሳናገኝ በኛ ገንዘብ መንግስት ለሌሎች ቤት ሰርቶ እየሰጠ ነው ይላሉ፡፡


ኮርፖሬሽኑ በበኩሉ በእነሱ ገንዘብ ሳይሆን በመንግስት አቅም የተገነቡ ቤቶችን ለልማት ተነሺዎች እንደተሰጠ ተናግሯል፡፡


በአዲስ አበባ ነዋሪ ከሚፈተንበት አንዱ ቤት ሲሆን ይህንን ችግር ለማሰስተካከል መንግስት የተቻለኝን ሁሉ እያደረግሁኝ ነው ይላል፡፡


ነዋሪዎች ደግሞ ቤት ለማግኘት ብለን ገንዘባችንን ለዓመታት ስንቆጥብ ብንቆይም መንግስት ቤቱን ሊያስረክበን አልቻልም የሚል ቅሬታን በተደጋጋሚ ሲያነሱ ይሰማሉ፡፡

ማርታ በቀለ


留言

無法載入留言
似乎有技術問題。請重新連線或重新整理頁面。
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page