top of page

ህገወጥ ደላሎች፤ ሰዎች በህገወጥ መንገድ ጉዞ ለመጀመር ሲያስቡ ወይም ህገወጥ ስደትን እዲያስቡ ከሚያደርጓቸው ከቀዳሚ ምክንያቶች መካከል ይጠቀሳል።

  • Jul 3
  • 1 min read

ሰኔ 26/2018


በየአካባቢው ያሉ ህገወጥ ደላሎች፤ ሰዎች በህገወጥ መንገድ ጉዞ ለመጀመር ሲያስቡ ወይም ህገወጥ ስደትን እዲያስቡ ከሚያደርጓቸው ከቀዳሚ ምክንያቶች መካከል ይጠቀሳል።


እነዚህ ደላሎች ኢትዮጵያውያኑ በህገ- ወጥ መንገድ ከሀገራቸው እንዲወጡ የተለያዩ ማማለያዎች በመጠቀም በሺዎች የሚቆጠሩትን አስወጥተዋል፡፡


ነገር ግን በዚሁ መንገድ ከሚወጡት ሰዎች መካከል የአውሬ እራት የሚሆኑ እና ካሰቡበት ሳይደርሱ መንገድ ላይ የሚቀሩትም ብዙ ናቸው፡፡


ይህንን ስራ የሚሰሩት ደላሎችም ቢሆኑ ለህግ ሲቀርቡ እንደማይስተዋል የተነገረ ሲሆን ማህበረሰቡ ቢያውቃቸውም ደፈር ብሎ ለህግ አካላት አሳልፎ የመስጠት ልምድ እንደሌለውም በጉዳዩ ላይ የሚሰሩ ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡


ህገወጥ ደላሎች ህግ ፊት ለማቅረብ ማህበረሰቡ እንዲጠቁም ለማድረግ ቢሞክርም ያ ሲሆን እንደማይስተዋል ያስረዳሉ፡፡


ህገወጥ ደላሎቹ በተለይ በገጠሪቱ የሀገሪቱ አካባቢ በሚገባ እየታወቁ ነዋሪው የማይጠቁምበት ምክንያት ምንድን ነው ስንል የጠየቅናቸው የማህበራዊ ጥናት መምህር እና ተመራማሪው ሎምቤቦ ታገሰ(ዶ/ር) ነዋሪው ቢጠቁም እንኳን ተመጣጣኝ ቅጣት ስለማይጣልባቸው ፍራቻ ላይ ይወድቃሉ ብለዋል።


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….


ፋሲካ ሙሉወርቅ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…









Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page