top of page

ህዳር 9፣2017 - የአለም አራት ኮኮብ አየር መንገድ ደረጃ ዕውቅና እና ሽልማት ማግኘቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Nov 18, 2024
  • 1 min read

የአለም አራት ኮኮብ አየር መንገድ ደረጃ ዕውቅና እና ሽልማት ማግኘቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተናገረ፡፡


አየር መንገዱ በዓመታዊው APEX Passenger Choice Awards 2025 የአለም አራት ኮኮብ አየር መንገድ ደረጃ ዕውቅና እና ሽልማት አግኝቻለሁ ብሏል፡፡


ይህ የአለም አራት ኮኮብ አየር መንገድ ሽልማት ከአንድ ሚሊዮን በላይ ከተረጋገጡ ጉዞዎች ከበረራ በኋላ ከመንገደኞች በተሰጡ ድምፆች መሰረት የተበረከተ መሆኑንም አስረድቷል፡፡

ሽልማቱ እና እውቅናው በአቪዬሽኑ ዘርፍ አለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ነው ሲል የኢትዮጵያ አየር መንገድ በማህበራዊ የትስስር ገጹ ላይ አስፍሯል፡፡


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page