top of page

ህዳር 6፣ 2017 - በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነበሩ ከተባሉ ኢትዮጵያዊያን መካከል አድራሻቸው የተገኘ ዜጎችን እንዲመለሱ ማድረጉ ተነገረ

በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እና እንደባሪያ ሊሸጡ ነበሩ ከተባሉ ኢትዮጵያዊያን መካከል አድራሻቸው የተገኘ ዜጎችን መንግስት ወደ ሀገር እንዲመለሱ ማድረጉ ተነገረ፡፡


እስካሁንም 31 ሰዎች አድራሻቸው መታወቁ ተሰምቷል፡፡


ባለፉት ወራት በህገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች የታየውና የኢትዮጵያ መንግስት የስራ ስምሪት ወዳልፈረመባት ማይናማር ዜጎች ተወስደው እንደባሪያ ይሸጡ እንደነበር ሲነገር ቆይቷል፡፡


የኢትዮጵያ መንግስት በማይናማር ኤምባሲ ስለሌለው በአካባቢ ሀገራት ባሉ ዲፕሎማቶች አማካይነት በተሰራ ስራ አድራሻቸው የተገኙ ዜጎችን ማስመለስ መቻሉን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ነቢያት ታደሰ ተናግረዋል፡፡


በማይናማር የሚገኙ እና አድራሻቸው ከታወቁ ዜጎች በተጨማሪ በሳውዲ አረቢያና በቤይሩት በአስቸጋ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎችን በተመሳሳይ መንግስት ወደ ሀገር እንዲመለሱ አድርጓልም ተብሏል፡፡




የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page