top of page

ህዳር 6፣ 2017 - ለቀድሞዋ ርዕሰ ብሔር ሳህለወርቅ ዘውዴ የምስጋና መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው

  • sheger1021fm
  • Nov 15, 2024
  • 1 min read

ለቀድሞዋ ርዕሰ ብሔር ሳህለወርቅ ዘውዴ የምስጋና መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።


የምስጋና ፕሮግራሙን ያዘጋጁት በበጎ ፍቃድ የተሰባሰቡ ሴቶችና በሴቶች የሚመሩ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች መሆናቸውን ሰምተናል።


ዝግጁቱም ፕሬዝዳንቷ በስራ ዘመናቸው ላከናወኗቸው ስራዎች ምስጋና ለማቅርብ ያለመ መሆኑ ተነግሯል።

የመጀመሪያዋ የኢፌዴሪ ሴት ፕሬዚዳንት የነበሩት ሳህለወርቅ ዘውዴ በፕሬዚዳንትነት ዘመናቸውና በዲፕሎማትነታቸው የሴቶችን አመራር ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ፣ የፆታ እኩልነት ለማስፈን እና ሴቶችን በሁሉም ዘርፍ ለማብቃት ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸው በዝግጅቱ ላይ ሲነገርላቸው ሰምተናል።


በተለይ በርካት ወጣት ሴቶች ወደ ሀላፊነት እንዲመጡ አስችሏል የተባለው ፕሬዚዴንሻል ኢኒሼቲቭ ፕሮግራም አበርክቶው የጎላ ሆኖ ሲጠቀስላቸው ሰምተናል።

ree

በመርሃ ግብሩ ላይ የቀድሞዋን ፕሬዝዳንት የህይወት ታሪክ የተመለከተና በመቅዲ ፕሮዳክሽን የተዘጋጀ አጭር ዶክመንተሪ ፊልም ቀርቧል።


ከዚህ በተጨማሪም የቀድሞዋን ፕሬዚዳንት እና ዲፕሎማት ሳህለወርቅ ዘውዴን በስራ አጋጣሚ የሚያውቋቸው አምሳደር ቆንጂት ስነጊዮርጊስ፣ ብሌን ወርቁ፣ ወ/ሮ ኢትዮጵያ ጥላሁን፣ ስኂን ተፈራ፣ ወ/ሮ ፅጌ ኃይሌ እና ሌሎች ምስክርነት ሰጥተዋል።


በሸራተን አዲስ በተካሄደው ዝግጅቱ ላይ አብረዋቸው የሰሩ ሰዎች ፣ የሴት ማሀበራት ተወካዮች ፣ ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል።

ree

በ1942 በአዲስ አበባ ተወልደው ያደጉት የቀድሞዋ ረዕሰ ብሔር ሳህለወርቅ ዘውዴ በጅቡቲ፣ በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም ተወካይ ሆነው ሰርተዋል።


በኬንያ የተባበሩት መንግሥታት ዳይሬክተር ጄነራል ሆነው መስራታቸውም ይታወሳል።


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page