top of page
  • sheger1021fm

ህዳር 30፣ 2015- ቁርጥራጭ ብረቶችን፣ የሚወገዱ ተሽከርካሪዎችንና ማሽኖችን ገዝተው የሚወስዱ አቅላጭ ፋብሪካዎች ለነዳጅና ለማጓጓዣ የሚያወጡት ወጪ ተቀናሽ

ህዳር 30፣ 2015


ቁርጥራጭ ብረቶችን፣ የሚወገዱ ተሽከርካሪዎችንና ማሽኖችን ገዝተው የሚወስዱ አቅላጭ ፋብሪካዎች ለነዳጅና ለማጓጓዣ የሚያወጡት ወጪ ተቀናሽ ሆኖ ይመለስላቸዋል ተባለ፡፡


ሐገር ቤት ያሉት የብረታ ብረት አምራቾች ያለ አገልግሎት የተከማቹ ቁርጥራጭ ማሽነሪዎችን ሲገዙ ለነዳጅና ለማጓጓዣ የሚያወጡት ወጪ እንዲመለስላቸው የአሰራር ማሻሻያ መደረጉን የማዕድን ሚኒስቴር ነግሮናል፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ብረት አቅላጭ ፋብሪካዎች የጥሬ እቃ ፍለጋ ከውጭ ሀገር ማስገባት ሳይኖርባቸው ሐገር ቤት ያለውን የወደቀ ሀብት እንዲጠቀሙ መንግስት ወስኗል ተብሏል፡፡


እነዚሁ የብረታ ብረት አቅላጭ ፋብሪካዎች ከሁሉም የመንግስት የልማት ድርጅቶች ያለአገልግሎት የተከማቹ ስቲል ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን በኪሎ በ64 ብር፤ ካስት አይረኖችን ደግሞ በኪሎ 51 ብር ከ75 ሳንቲም ከፍለው ማንሳት እንደሚችሉ ተሰምቷል፡፡


መወገድ ያለባቸውን ተሽከርካሪዎች፣ ማሽነሪዎች እና ያገለገሉ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎችን ደግሞ ለኪሎ 51 ብር ከ25 ሳንቲም ይጠየቃሉ ተብሏል፡፡


አልሙኒየም ብረታ ብረቶችን ደግሞ በኪሎ 120 ብር ከፍለው እንዲወስዱ የማዕድን ሚኒስቴር ለሚመድባቸው የብረታ ብረት አቅላጭ ኢንዱስትሪዎች እንዲያስተላልፉ ወስኗል፡፡


እነዚሁ ቁርጥራጭ ብረቶችና ማሽነሪዎችን የሚወስዱ የብረታ ብረት አቅላጭ ኢንዱስትሪዎች ወደ ፋብሪካቸው ሲወስዱ የሚያወጡት የትራንስፖርት ነዳጅ ወጪ ተቀናሽ ይደረግላቸዋል ተብሏል፡፡


ንብረቱን ለማስመዘን የሚያወጧቸውንም የማስመዘኛ ወጪዎች ተቀናሽ ተደርጎ እንዲሸጥላቸው መወሰኑ ተሰምቷል፡፡


የብረት አቅላጭ ፋብሪካዎቹ እነዚህን ወጪዎች

በሰነድ አስደግፈው ሲያቀርቡ ጠቅላላ ከሚከፍሉት ክፍያ ላይ ተቀናሽ ተደርጎ እንዲሸጥላቸው እና ቀሪው ገንዘብ ወደ ማዕከላዊ ግምጃ ቤት እንዲገባ መወሰኑንም የማዕድን ሚኒስቴር ለሸገር ነግሯል፡፡


ተህቦ ንጉሴ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz



Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page