top of page

ህዳር 3፣ 2017 - ''የተሽከርካሪዎች የጭነት ክብደት መጠን ለመወሰንና ለመቆጣጠር ተብሎ የወጣው ደንብ የኑሮ ውድነቱን ያባብሰዋለል'' የተሽከርካሪ ባለንብረቶች

  • sheger1021fm
  • Nov 12, 2024
  • 1 min read

የተሽከርካሪዎች የጭነት ክብደት መጠን ለመወሰንና ለመቆጣጠር ተብሎ የወጣው ደንብ የኑሮ ውድነቱን ያባብሰዋለል በሚል የተሽከርካሪ ባለንብረቶች ተቃውሞ አቀረቡ።


የተሽከርካሪዎችን የጭነት ክብደት መጠን ለመወሰን እና ለመቆጣጠር የወጣው ደንብ አንድ ተሽከርካሪ ከ350 ኩንታል ወይም ከ35 ቶን በላይ መጫንን የሚከለክል ነው።


በዚህ ጉዳይ ላይ ያነጋገርናቸው የተሽከርካሪ ባለንብረቶችም የተሽከርካሪ የጭነት ክብደት መጠን ገደብ መጣሉ ለተሽከርካሪዎች እና ለመንገዶች ደህንነት ታስቦ ቢሆንም የጭነት መጠኑ ላይ የተወሰነ መሻሻል መደረግ አለበት ብለዋል።


ይህ ካልሆነ ግን የኑሮ ውድነቱን ያባብሰዋል ሲሉ ነግረውናል።


የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር አለሙ ስሜ በተሽከርካሪዎች ላይ የወጣው የክብደት መጠን ወሰን ለተሽከርካሪዎች እና ለመንገዶች ደህንነት ታስቦ ነው፤ የልኬት መጠኑም የተጋነነ አይደለም ብለዋል።


ፍቅሩ አምባቸው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page