top of page

ህዳር 3፣ 2017 - በየቦታው በሚጠየቅ የተሽከርካሪ የኮቴ ክፍያ ምክንያት የተሽከርካሪ ባለንብረቶች መማረራቸውን ተናገሩ

በየቦታው በሚጠየቅ የተሽከርካሪ የኮቴ ክፍያ ምክንያት የተሽከርካሪ ባለንብረቶች መማረራቸውን ተናገሩ፡፡


በየመንገዱ #ኬላ እየዘረጉ ገንዘብ የሚጠይቁ ከጊዜ ወደ ጊዜም እየጨመሩ መሆናቸውም ተናግረዋል።


የፀጥታ ችግር ያለባቸው አካባቢዎች ላይ ችግሩ ይሰፋልም ሲሉ ነግረውናል።


በየጊዜው የሚጠየቀው የኮቴ ክፍያ እና በሽከርካሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው እንግልት፣ ምርቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዳይገቡ መስተጓጎል ከመፍጠር፣ በየጊዜው የሚጠየቀው ክፍያ ማሻቀብም ምርቶች ላይ #ዋጋ እንዲጨምር ያደርጋል ብለዋል።


የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር በበኩሉ #የኮቴ_ክፍያ ህገ-ወጥ ስለሆነ እንዲቀርም ከክልሎች ጋር እየተናገርን ነው ብሏል፡፡


ፍቅሩ አምባቸው

Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page