top of page
  • sheger1021fm

ህዳር 27፣ 2015- ጎሕ ቤቶች ባንክ ስራ በጀመረበት 2014 በጀት ዓመት 8 ወራት ያልተጣራ 7.9 ሚሊየን ብር ማትረፉን ተናገረ

ህዳር 27፣ 2015


ቤት ገዢዎችን፣ ገንቢዎችን፣ አዳሾችን በገንዘብ መደገፉ ዋናው ዓላማው አድርጎ የተቋቋመው ጎሕ ቤቶች ባንክ ስራ በጀመረበት 2014 በጀት ዓመት 8 ወራት ያልተጣራ 7.9 ሚሊየን ብር ማትረፉን ተናገረ፡፡


ከትርፉ ላይ ህጋዊ መጠባበቂያ፣ የረጅም ጊዜ የግብር ዕዳ ወጪ ማስተካከያ እንዲሁም ለብድርና ተሰብሳቢዎች የሚያዝ ተጨማሪ መጠባበቂያ ሲቀነስለት የተጣራ 2.4 ሚሊየን ብር አግኝቻለሁ ብሏል፡፡


ባንኩ በዛሬው ዕለት የመጀመሪያውን ጠቅላላ ጉባኤ አካሂዷል፡፡


በጉባኤው ላይ የባንኩን የ2014 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ያቀረቡት የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢው አቶ ጌታሁን ናና ባንኩ ስራ በጀመረ 8 ወራት ውስጥ ያገኘው ውጤት አበረታች ነው ብለዋል፡፡


በዚህም የባንኩ ተቀማጭ 256.6 ሚሊየን ብር፣ በብድር እና ቅድመ ክፍያ የተሰጠ 298.5 ሚሊየን ብር እንዲሁም ጠቅላላ ገቢው ደግሞ 121.7 ሚሊየን ብር መሆኑንን የቦርድ ሰብሳቢው አስረድተዋል፡፡


የጎሕ ቤቶች ባንክ አጠቃላይ ሀብት 1.2 ቢሊየን ብር፣ የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ 780 ሚሊየን ብር መሆኑንን ሰምተናል፡፡


በኢትዮጵያ የቤት ፍላጎቱ ከፍተኛ መሆኑንን የተናገሩት የቦርድ ሰብሰቢው የባንኩ የማደግ እድልና አቅም ከፍተኛ መሆኑንን ተናግረዋል፡፡


ይሁን እንጂ ለቤቶች ብድር የሚውል የረጅም ጊዜ ገንዘብ ማሰባሰብ ለባንኩ ከፍተኛ ችግር ሆኖበታል ብለዋል፡፡


በኢትዮጵያ በተለይ በአዲስ አበባ መሬት ማግኘት ፈታኝ መሆኑን ያነሳው ጎሕ ቤቶች ባንክ ዜጎች የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ይህንን የመሬት አቅርቦት ችግር ለመፍታት ከመንግስት ጋር እየተነጋገርኩ ነው ሲል ሰምተናል፡፡


ጎሕ ቤቶች ባንክ ከሁለት ዓመት በ


ኋላ የተከፈለ ካፒታሉ አሁን ካለበት በእጥፍ ያህል አድጎ 1 ቢሊየን ብር አንዲሆን ወስኗል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page