top of page

ህዳር 27፣ 2015- የኢንዶኔዥያ ፓርላማ ከጋብቻ ውጭ የሚደረግን ወሲባዊ ግንኙነት የሚነውር ህግ አፀደቀ፡፡

ህዳር 27፣ 2015


የኢንዶኔዥያ ፓርላማ ከጋብቻ ውጭ የሚደረግን ወሲባዊ ግንኙነት የሚያነውር ህግ አፀደቀ፡፡


ሕጉ ከጋብቻ ውጭ ወሲብ የሚፈፅሙት በ1 ዓመት እስር እንዲቀጡ የሚጠይቅ እንደሆነ ኢቭኒንግ ስታንዳርድ ፅፏል፡፡


የሕጉ የተፈፃሚነት ወሰን ወደ ኢንዶኔዥያ የሚገቡ አገር ጎብኚ ቱሪስቶችንም ይመለከታል ተብሏል፡፡


ሕጉ አሁን ቢፀድቅም ተፈፃሚነቱ እንደሚዘገይ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


ሕጉን ሥራ ላይ ማዋሉ በጥቂቱ የአመት ጊዜ ሊጠይቅ ይችላል ተብሏል፡፡


የሕጉ ሥራ ላይ መዋያ የሚዘገየው የማስፈፀሚያ ደንብ እና መመሪያዎችን ለማሰናዳት ሲባል መሆኑ ታውቋል፡፡


የኔነህ ከበደ



ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page