top of page

ህዳር 27፣ 2015- የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪዎች እና ተቃዋሚዎቻቸው አገሪቱን ወደ ህዝባዊ አስተዳደር ለመመለስ በሚደረገው ሽግግር ላይ ተስማሙ፡፡

ህዳር 27፣ 2015


የሱዳን ወታደራዊ መንግስት መሪዎች እና ተቃዋሚዎቻቸው አገሪቱን ወደ ህዝባዊ አስተዳደር ለመመለስ በሚደረገው ሽግግር ላይ ተስማሙ፡፡


ሽግግሩ በአገሪቱ ምርጫ እስኪካሄድ ለ2 ዓመታት እንደሚዘልቅ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡


ከጦር አለቆቹ ጋር ስምምነቱን ከተፈራረሙት መካከል የነፃነት እና የለውጥ ሀይሎች የተሰኘው ጥምረት አንዱ መሆኑ ታውቋል፡፡


ስምምነቱን ያልፈረሙ የተቃውሞ ሀይሎች እንዳሉ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


የስምምነቱ ተቃራኒዎች የተቃውሞ ሰልፍ መጥራታቸው ተሰምቷል፡፡


የሱዳን የጦር አለቆች ከአመት በፊት ዳግም ግልበጣ ከፈፀሙ በኋላ አገሪቱ በፖለቲካዊ ቀውስ ስትናጥ መቆየቷን ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ



ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page