top of page

ህዳር 26፣2017 - ጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ፤ 94 ስደተኞችን በአውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Dec 5, 2024
  • 1 min read

ጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ፤ 94 ስደተኞችን በአውሮፕላን ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን ተናገረ፡፡


ስደተኞቹ እንዲመለሱ የተደረገው በጀቡቲ ከሚገኘው የዓለም አቀፍ ፍልሰተኞች ድርጅት (IOM) ጋር በመተባበር ነው ብሏል ኤምባሲው፡፡


ኤምባሲው በህገወጥ መንገድ ድንበር መሻገርን በመተው የሰዎችን ህይወት መቀጠፍ መቀነስ እንደሚያስፈልግም አሳስቧል፡፡

ከኢትዮጵያ ተነስተው በጀቡቲ በማድረግ ወደ ሌሎች ሀገራት ለመሻገር የሚሞክሩ ሰዎች ብዙ እንደሆኑ ይነገራል፡፡


በዚህም የጀልባ የመገለበጥ አደጋ አጋጥሞ ስደተኞች ህይወታቸውን እንደሚያጡ IOM በተደጋጋሚ የሚያወጣቸው መግለጫዎች ያሳያሉ፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page