top of page

ህዳር 26፣2017 - ዘምዘም ባንክ ከሳንቲም ፔይ ፋይናንሻል ሶሉሽንስ ጋር አብሮ ለመስራት ተስማማ

  • Dec 5, 2024
  • 1 min read

ዘምዘም ባንክ ከሳንቲም ፔይ ፋይናንሻል ሶሉሽንስ ጋር አብሮ ለመስራት ተስማማ።


ስምምነቱን የባንኩና የሳንቲምፔይ ሃላፊዎች በዛሬው እለት ተፈራርመውታል፡፡


ስምምነቱ የዘምዘም ባንክ ደንበኞች ለሚፈፅሙት ግብይት እና ለተጠቀሙት አገልግሎት በቀላሉ በሳንቲምፔይ በኩል ክፍያ መፈፀም የሚያስችላቸው ነው ተብሏል።


አገልግሉቱን ለማግኘትም ሳንቲምፔይ በየንግድ ማዕከላት ያከፋፈላቸውን ኪውአር ኮድ በተቀሳቃሽ የእጅ ስልካ ስካን በማድረግ በቀላሉ ክፍያ መፈፀም የሚያስችል መሆኑ ተነግሯል።

ይህም በጤና ተቋማት፣ በአልባሳት ደብሮች፣ በስጦታ ዕቃ መደብሮች፣ ግባታ ዕቃ መሸጫዎች፣ የኤሌክትኒክስ መሸጫዎች፣ በስቴሽነሪዎች፣ በመኪና ዕቃ እና ጌጣ ጌጥ መሸጫዎች፣ ሆቴሎች እና በካፌዎች እና ሌሎችም በርካታ አገልግሎት ቦታዎች ደንበኞችን ለተጠቀሙት አገልግሎት እንዲሁም ለፈጸሙት ግዢ በተንቀሳቃሽ የእጅ ስልካቸው ብቻ ክፍያ መፈጸም እንደሚችሉ በስምምነት ስነስርዓቱ ላይ ተነግሯል።


አገልግሎቱ ክፍያን ከማቅለል በተጨማሪ ደንበኞች ካሉበት ሆነው የተለያዩ ክፍያዎችን መፈጸም ያስችላቸዋልም ሲብል ሰምተናል።


ዘምዘም ባንክ በሙሉ በሙሉ ከወለድ ነጻ ባንክ አገልግሎት የሚሰጥ ባንክ ነው፡፡


ሳንቲምፔይ ክፍያዎችን ለመፈጸም እና ሌሎች አስፈላጊ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማቅረብ የሚያስችል የክፍያ መፈጸሚያ መድረክ ነው።


አሁን ላይ በክፍያ መፈጸሚያ መድረኩ ቢያንስ አንድ ጊዜ የገንዘብ ዝውውር ያደረጉ ከ8 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉኝ ብሏል፡፡



Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page