top of page

ህዳር 26፣2017 - ህጋዊ መሆኑን ያረጋገጠው የአባይ ውሃ የትብብር ማዕቀፍ (CFA) ለአንዳንድ ሀገራት አዲስ ፍላጎትን የጫረ ይመስላል ተባለ

ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ ህጋዊ መሆኑን ያረጋገጠው የአባይ ውሃ የትብብር ማዕቀፍ (CFA) ለአንዳንድ ሀገራት አዲስ ፍላጎትን የጫረ ይመስላል ተባለ፡፡


የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫቸው ህጋዊነቱን ያረጋገጠውን የኮፕሬቲቭ ፍሬም ወርክ አግሪመንት ወይም #CFA በትብብር መቀበሉ ለሁሉም ሀገራት ይበጃል ያልፈረሙ ሀገራትም ቢቀላቀሉ ይሻላል ይህ ሳይሆን ግን በጉዳዩ ዙሪያ አዳዲስ ህጋዊ ያልሆኑ መንገዶችን መከትል ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡


ከሶማሊያ ሪፖብሊክ በኩል የማያባራ ትንኮሳ እና ዛቻ ወደ ኢትዮጵያ እየተሰማ ነውና በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ግን ምላሽ ሲሰጥ አይሰማም የተባሉት አምባሳደር ነቢያት ‘’ሀላፊነት የሚሰማን ስለሆነ ነገሮችን ማባባስ አንፈልግም’’ ብለዋል፡፡


የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በወቅታዊ ጉዳዮች መግለጫቸው በዜጋ ተኮር፣ ዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ልዩ ልዩ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል፡፡


የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page