top of page

ህዳር 20፣2017 - የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ብክለቱን ማቆም ካልቻለ ከቦታው እንዲነሳ በፍርድ ቤት ተወሰነበት

  • sheger1021fm
  • Nov 29, 2024
  • 1 min read

ከ30 ዓመታት በላይ አካባቢ ሲበክልና ለሰው ጤና ጎጂ የሆነ በካይ ፍሳሽ ቆሻሻ በዘፈቀደ ሲለቅ ነበር የተባለው የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ብክለቱን ማቆም ካልቻለ ከቦታው እንዲነሳ በፍርድ ቤት ተወሰነበት፡፡


ለሕዝብ ጥቅም ሲባል በፍርድ ቤት ተቋሙን ላይ ክስ በመመስረትና ለ5 ዓመታት በመሞገት የተጠቀሰው ውሳኔ እንዲሰጥ ምክንያት የሆነው ‘’ቁም ለአካባቢ’’ የተሰኘ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው፡፡


በጎ ፈቃደኛ የህግ ባለሞያዎች የአካባቢ ብክለትን በተመለከተ መሰል ስራዎችን የሚከውነው ቁም ለአካባቢ፤ ከዚህ ቀደምም በ7 ተቋማት ላይ ተመሳሳይ ውሳኔ በፍርድ ቤት መገኘቱን ነግሮናል፡፡


የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ብክለቱተን ማቆም ካልቻለ አሁን ካለበት ቦታ ተነስቶ ሌላ ቦታ ላይ ደረጃውን የጠበቀና ዘመናዊ የእንስሳት እርድ የሚከውነበት ቦታ እንዲያዘጋጅ በፍርድ ቤት ተወስኖበታል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….


ትዕግስት ዘሪሁን


Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page