top of page

ህዳር 18፣2017 - ''መንግስታዊ ተቋማት ሳይቀር ስራዬን በአግባቡ እንድሰራ እየፈቀዱልኝ አይደለም'' የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባልስጣን

  • sheger1021fm
  • Nov 27, 2024
  • 1 min read

መንግስታዊው የአዲስ አበባ የአካባቢ ጥበቃ ባልስጣን ተቋማት የአካባቢ ብክለት ፈፅመው መሆኑን ወይም አለመሆኑን ለማረጋገጥ ስሄድ ወደ ግቢያቸው እንኳን እንዳልገባ እየተከለከልኩ ነው አለ፡፡


መንግስታዊ ተቋማት ሳይቀር ስራዬን በአግባቡ እንድሰራ እየፈቀዱልኝ አይደለም ብሏል፡፡


የአካባቢ ተፅእኖ ግምገማ ሳይደረግባቸው የንግድ ፈቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ የሚሰጡ ተቋማት ስራችንን እያወኩት ነውም ሲል ባለስልጣኑ ተናግሯል።


የአካባቢ ብክለትን ለመከላከል ህጉን ተላልፈው በተገኙት ላይ ባለስልጣኑ የሚወስደውን እርምጃ ባለስልጣኑን የልማት አደናቃፊ አድርገው የሚቆጥሩት አንዳንድ ተቋማት እንዳሉም ተነግሯል።


የባለስልጣኑ የአካባቢ ጥበቃ የህግ ተከባሪነት ዳይሬክተር አቶ ለሜሣ ጉደታ በከተማዋ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ኢንዱስትሪዎች አይደለም የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሊደረግባቸው ምን እንደሚያመርቱ እንኳን የማናውቅበት ደረጃ ላይ ደርሰናል ብለዋል።

በቦታው ግምገማ ለማድረግ ሲኬድም ለእኛ በራቸው ዝግ እየሆነ ተቸግረናል ብለዋል፡፡


የድምጽ ብክለት ደረጃውን ባለፉ ዳንኪራ ቤቶች ላይ የማሸግ እና ፍቃድ የመሰረዝ እርምጃ እየወሰድን ቢሆንም ንግድ ቢሮ ስራችንን ማገዝ ሲገባው እርምጃ በተወሰደበት ቤት ላይ በሌላ ሰው ስም ሌላ ፍቃድ እንዲሰጥ በማድረግ ስራችን ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ እንዲሆን አድርጓል ሲሉ አቶ ለሜሣ ጉደታ ነግረውናል።


ከንግድ ቢሮ ባለፈም ባህል ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ላልተደረገባቸው ምሽት ቤቶች እና ለከፍተኛ ድምፅ ብክለት አጋላጭ በሆኑ ትላልቅ ፎቆች ውስጥ ላሉ ዳንኪራ ቤቶች የብቃት ማረጋገጫ እየሰጠ መሆኑንም አቶ ለሜሣ ተናግረዋል።


ትናንት በጉዳዩ ላይ ውይይት ሲደረግ ቅሬታ የቀረበባቸው የተጠቀሱት ተቋማት የተገኙ ቢሆንም ምላሽ ግን ሳይሰጡበት አልፈዋል፡፡

ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page