ህዳር 13፣2017 - ኢትዮፒካር፤ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ 3 ‘’የኔታ ብራንድ’’ ተሽከርካሪዎች ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረብ መጀመሩን ተናገረ
- sheger1021fm
- Nov 22, 2024
- 1 min read
በኢትዮፒካር በኩል ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡትን የኔታ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን የሚያመርተው "ሆን ዞ" የሚባለው የቻይና ኩባያ ነው፡፡
የሆን ዞ የኢትዮጵያና ምስራቅ አፍሪካ ብቸኛ ወኪል የሆነው ኢትዮፒካር ወደ ሀገር ቤት እያስመጣቸው ያሉት ሶስቱ የኔ ምርቶች ኔታ ዩ (NETA U)፣ ኔታ አያ (NETA Aya) እንዲሁም ኔታ ኤክስ(NETA X) የሚባሉ ናቸው፡፡
ተሽከርካሪዎቹ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተዘጋጀው እና ዛሬ በተከፈተውና እስከ ህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በሚቆየው የ"ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2024" ኤግዚቢሽን እና አለም አቀፍ ሲምፖዚየም ላይ ቀርበዋል፡፡


በዚህ "ኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ 2024" ኤግዚቢሽን ላይ አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት እና የውጭ ሃገራት ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን ኢትዮፒካር ያቀረባቸውን የኔታ ብራንድ ምርቶችን በመጎብኘት አድናቆት ሰጥተዋል፣ አበረታትተዋል፡፡
ኢትዮፒካር እነዚህን የኔታ ብራንድ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች አንደሚያከፋፍልም አስረድቷል፡፡
ኢትዮፒካር ከዚህ በፊትም የተለያዩ ዓይነት ተሽከርካሪዎችን ከውጪ ሃገር ሲያስመጣ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comments