top of page

ህዳር 10፣2017 - የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ የአቶ ሰዒድ ዓሊ ከማል ያለመከሰስ መብት ተነሳ

የአዲስ አበባ ምክር ቤት የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑትን፤ የአቶ ሰዒድ ዓሊ ከማል ያለመከሰስ መብትን አነሳ፡፡


ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው የምክር ቤቱ አባል በሙስና መጠርጠራቸው ተነግሯል፡፡


የአዲስ አበባ ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው፡፡


የምክር ቤቱ አባልና የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑትን የአቶ ሰዒድ ዓሊ ከማል ያለመከሰስ መብትን የተነሣው በፍትሕ ሚኒስቴር በቀረበ ጥያቄ መሠረት መሆኑን በምክር ቤቱ የሰላም፣ የፍትሕ እና መልካም አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ ተናግሯል።

ቋሚ ኮሚቴው በሚኒስቴሩ የቀረበውን የሙስና ክስ በመመርመር የደረሰበትን ውጤት ለምክር ቤቱ ዝርዝር ሪፖርት አቅርቧል።


ምክር ቤቱ የቀረበው ሪፖርትን በመመልከት፤ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በሕግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ በሙሉ ድምፅ ወስኗል፡፡


ያሬድ እንዳሻው



コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page