top of page

ህዳር 10፣2017 - በ615 ወረዳዎች አጀንዳ መሰበሰቡን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Nov 19, 2024
  • 1 min read

እስካሁን ከ615 ወረዳዎች አጀንዳ መሰበሰቡን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተናገረ፡፡


ኮሚሽኑ ይህን የተናገረው ዛሬ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የስራ ክንውን ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡


በተያዘው ወር በኦሮሚያ ክልል ካሉ ከ360 ወረዳዎች አጀንዳዎችን ተሰብስቦ እንደሚጠናቅቅ የኮሚሽኑን የክንውን ሪፖርት ያቀረቡት ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ(ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

ኮሚሽነሩ ‘’በትጥቅ ግጭት ውስጥ ባለው የአማራ ክልልም መቶ በመቶ የተባባሪ ልየታ አድርገናል’’ ያሉ ሲሆን በክልሉ ባሉ 267 ወረዳዎቸው አጀንዳ መሰብስብ እንደሚጀመር አስረድተዋል፡፡


ኮሚሽኑ በትግራይ ክልልም በቅርቡ ስራ እንደሚጀመር ጠቁሟል፡፡


ኮሚሽነር መስፍን አርአያ በሀገሪቱ ከ1,400 በላይ ወረዳዎች መኖራቸውን ተናግረው እስካሁን ከ612 ወረዳዎች አጀንዳ ተሰብስቧል ሲሉ አስረድተዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page