top of page

ህዳር 10፣2017 - በ2017 የትምህርት ዘመን ለመመዝገብ ከታቀደው የተማሪ ቁጥር የተመዘገበው በ10 ሚሊዮን ያነሰ እንደሆነ ተነገረ

  • Nov 19, 2024
  • 1 min read

በ2017 የትምህርት ዘመን ለመመዝገብ ከታቀደው የተማሪ ቁጥር የተመዘገበው በ10 ሚሊዮን ያነሰ እንደሆነ ተነገረ።


በመላ ሀገሪቱ በ2017 የትምህርት ዘመን ከቅድመ መደበኛ እስከ 2ኛ ደረጃ ባሉ ትምህርት ቤቶች ከ32 ሚሊዮን በላይ #ተማሪዎች ለመመዝገብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የተመዘገቡት ግን 21 ሚሊዮን 723 ሺህ ነው ተብሏል።


ቁጥሩ ከታቀደው የቀነሰው በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ነው ተብሏል።


ይህ የተነገረው በህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት የሰው ኃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የትምህርት ሚኒስቴርን የበጀት ዓመቱ የ3 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም በተመለከተ ከመሥሪያ ቤቱ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው።


ወደ #መምህርነት ሞያ የሚገቡ ሰዎችን ቁጥር ዝቅተኛ መሆኑን በውይይቱ ወቅት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል።


ይህንን ለማስተካከል የተለያዩ የማትጊያ ሥርዓቶች ይዘረጋሉ ብለዋል።


#የመምህራን_ባንክ የማቋቋም ሀሳብ መኖሩን

ከነዚህ  አንዱ እንደሆነ ጠቅሰዋል።


ይህም መምህራን በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸው የሚያስችል ነው ተብሏል።


የትምህርት ጥራትን ለማሳደግ እንደ ሀገር  የመምህራን ብቃት በረዥም ጊዜ ዕቅድ ሊሰራበት እንደሚገባም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።


የመምህራንን አቅም ለመገንባት ከ44,000 በላይ መምህራን ሥልጠና መሰጠቱንም አስረድተዋል።

የትምህርት ጥራትን ችግርን ለመቅረፍ በመንግሥትና #በግል_ትምህርት_ቤቶች መካከል ያለውን ልዩነት ማጥበብ ይገባልም ብለዋል።


ትምህርት ሚኒስቴር፤ የዩኒቨርቲዎችን የተማሪ ቁጥር ለመጨመር ብሎ የትምህርት ጥራትን ጥያቄ ውስጥ አልከትም ብሏል።


በተያያዘም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች፤ በተማሪዎች ምገባ ተጠቃሚ እንደሆኑ ተጠቅሷል።


የሁለተኛ ደረጃ የተማሪ መፅሐፍት በሁሉም ክልሎች 1 መፅሐፍ ለአንድ ተማሪ የማዳረሱ ስራም ትኩረት ከተሰጧቸው ስራዎች መካከል ነው ሲል የእንደራሴዎች ምክር ቤት ተናግሯል።


ማንያዘዋል ጌታሁን

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page