top of page

ህዳር 10፣2017 - በሶማሌላንድ በቅርቡ በተካሄደው ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ የተቃዋሚ መሪው ሞሐመድ አብዱላሂ አሸነፉ

  • sheger1021fm
  • Nov 19, 2024
  • 1 min read

በሶማሌላንድ በቅርቡ በተካሄደው ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ የተቃዋሚ መሪው ሞሐመድ አብዱላሂ አሸነፉ፡፡


ሞሐመድ አብዱላሂ በምርጫው ማሸነፋቸውን የሀገሪቱ የምርጫ አከናዋኝ መስሪያ ቤት እወቁልኝ ማለቱን አሶሼትድ ፕሬስ ፅፏል፡፡


የተቃዋሚ መሪው በምርጫው ያሸነፉት ከተሰጠው ድምፅ ከ50 በመቶ በላይ የሆነውን በማግኘት ነው ተብሏል፡፡


በስልጣን ላይ የሚገኙት ፕሬዘዳንት ሙሴ ቢሒ ከተሰጠው ድምፅ ያገኙት 30 በመቶ ያህሉን እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡


ሙሴ ቢሒ ላለፉት 7 ዓመታት ስልጣን ላይ ቆይተዋል ተብሏል፡፡


ሶማሌላንድ ራሷን ከተቀረችዋ ሶማሊያ ከነጠለች 33 ዓመታትን እንዳስቆጠረች መረጃው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page