ህዳር 10፣2017 - ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን 55 የፖለቲካ ፓርቲዎች አብረውት እየሰሩ መሆኑን ተናገረ
- sheger1021fm
- Nov 19, 2024
- 1 min read
ብሔራዊ መግባባትን ለማምጣት በሚከወነው ሀገራዊ ምክክር 55 የፖለቲካ ፓርቲዎች አብረውት እየሰሩ መሆኑን ተናገረ፡፡
ይሁንና ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጋር አብሮ ለመስራት በፈረሙ ማግስት ለእስር የሚዳረጉ እንዳሉ አቤቱታ ያቀርቡልናል ሲሉ ዋና ኮሚሽነሩ ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ተናግረዋል፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ የኮሚሽኑን የስራ አፈፃፀም በተመለከተ ዛሬ በፓርላማ ተገኝተው ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያቀርቡልንን የተጠቀሰውን እና መሰል አቤቱታ ተቀብለን ችግሩን በተመለከተም ለሚመለከተው አካል ጥያቄውን አቅርበን የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋና አስቻይ ሁኔታ እንዲፈጠር እየሰራን ነው ብለዋል፡፡
ኮሚሽኑ በምክክር ብሔራዊ መግባባትን እንዲያመጣ የተሰጠው የስልጣን ጊዜ 3 ዓመት ሲሆን ሊጠናቀቅ የ3 ወራት እድሜ ቀርተውታል፡፡
ፕሮፌሰር መስፍንም አሁን ኮሚሽኑ ስራውን አጥጠናቆ የመውጫ ሪፖርቱን ለፓርላማው ማቅረብ የነበረበት ጊዜ እንደነበር ጠቅሰው በተለያዩ ክልሎች ያለው የፀጥታ ችግር ለስራው መጓተት ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ፓርላማው የኮሚሽኑን የስልጣን ጊዜ ካላራዘመለት ከ3 ወር በኋላ የተሰጠው የስልጣን ጊዜ ይጠናቀቃል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
Comments