ተፈሪ ዓለሙ በ“ትዝታ ዘ አራዳ” መሰናዶው ስለ “እድገት በሕብረት ዘመቻ” ይነግረናል…
አስተያየት ይፃፉ (0 አስተያየት)ማህበሩ 5 መቶ ሐኪሞች እንዳሉት የተነገረ ሲሆን አንድ መቶ ሚሊዮን ሕዝብ ላላት ኢትዮጵያ ቁጥሩ አናሳ ስለመሆኑ ተነግሯል፡፡አፍ፣ መተንፈሻ መመገቢያና ውበት ነው ያሉት ዶ/ር ሙሉዓለም ልዩ ጥንቃቄ በማድረግ ከሌሎች በሽታዎች ራሳችንን መጠበቅ እንችላለን ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ለ4ኛ ጊዜ የተከበረው የዓለም አቀፍ የአፍ ጤናን አጠባበቅን የዘንድሮ መሪ ሀሳብ “አፍዎ ስለ ጤና ይናገራል” የሚል ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲከበር ደግሞ ለ6ኛ ጊዜ ነው ተብሏል፡፡ማህበሩ ከዩኒሊቨር ጋር በመተባበር በእግረ መንገድ በጎ ስራም ከ25 ሺ ሚሊ ሊትር በላይ ደም መለገሱን ከማህበሩ ሰምተናል፡፡
ምስክር አወል
መድኃኒት ለተላመደ የቲቢ በሽታ ከተጠቁ ህሙማን ውስጥ እስካሁን 3 ሺ 889 የሚሆኑት ህክምናው እየተከታተሉ ነው፡፡የቲቢ በሽታን ጨርሶ ከኢትዮጵያ ለማጥፋትና ለመከላከል የገንዘብ እጥረት እክል እየፈጠረብኝ በመሆኑ የአጋር ድርጅቶችን ድጋፍ እሻለሁ ሲል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ የሚከበረው የቲቢ በሽታ ቀን፣ በሽታውን የመከላከል ስራዎች በመስራት፣ ቅድመ ምርመራ እንዲደረግ ግንዛቤ በመፍጠር እና በሽታውን ጨርሶ ለማጥፋት የተለያዩ የምርመር ስራዎች እየቀረቡ በኢትዮጵያ ይታሰባል መባሉን ሰምተናል፡፡
ምህረት ሥዩም
Audio clip: Adobe Flash Player (version 9 or above) is required to play this audio clip. Download the latest version here. You also need to have JavaScript enabled in your browser.
አስተያየት ይፃፉ (0 አስተያየት)Audio clip: Adobe Flash Player (version 9 or above) is required to play this audio clip. Download the latest version here. You also need to have JavaScript enabled in your browser.
‘ጫቱ ላይ ያለውን ተባይ ለማጥፋት እና ጫቱ ‘ሻይን’ እንዲያደርግ፣ እንዲያምር በሚል ዲዲቲ ይረጭበታል…’ ጫት ላይ የሚረጨው ዲዲቲ ነገር… ለወጣ ትንኝ ማጥፊያ በሚል ወደ ሐገራችን የገባው ዲዲቲ በአሁኑ ወቅት በሐገራችን በሕግ የተከለከለ ኬሚካል ቢሆንም ገበሬው ከሕገወጥ ሻጮች እየገዛ ጫት እና የተለያዩ የጓሮ አትክልቶች ላይ ይረጨዋል ይለናል ይህ የትዕግስት ዘሪሁን ዘገባ… በተለያዩ ሐገራት የተከለከለው ይህ ኬሚካል ለጉበት፣ ለነርቭ፣ ለካንሰር እና ለመሃንነት እንዲሁም የጤና እክል ያለባቸው ሕፃናት እንዲወለዱ ምክንያት ይሆናል ነው የሚባለው፡፡
ዘገባው እንደሚለው ጭራሽ አንዳንድ ገበሬዎች ለረጅም ጊዜ የሚያስቀምጡት በቆሎ ነቀዝ እንዳይበላው በሚል በዲዲቲ አሽተው ያስቀምጡታል… ይህን ለጤና አደገኛ የሆነ ኬሚካልን ገበሬዎች እንደማንኛውም ሸቀጥ በቀላሉ ማግኘት መቻላቸውና እንደልባቸው እንደፀረ-ተባይ ኬሚካል መጠቀማቸው ሊያስከትል የሚችለው ማህበራዊ የጤና ጠንቅ የትየለሌ ነው ነው የሚባለው፡፡
16 ሚሊየን ያህል ኢትዮጵያውያን የሚቅሙት ጫት ላይ ዲዲቲ የመረጨቱ ነገር አሳሳቢ ነው የሚለው ዘገባው፤ ጫቱ ላይ ያለውን ተባይ ለማጥፋት እና ጫቱ ‘ሻይን’ እንዲያደርግ፣ እንዲያምር በሚል ዲዲቲ ይረጭበታል ይላል፡፡ በጫቱ ቅጠል ውስጥ ሰርጎ የሚገባው ዲዲቲ ቢታጠብም አይወጣም የሚሉት ባለሞያ መርዛማው ኬሚካል አፈር ውስጥ ከ15 ዓመት፤ ውሃ ውስጥ ደግሞ ከ150 ዓመታት በላይ ይቆያል ይላሉ…ሙሉውን ያዳምጡ
ትዕግስት ዘሪሁን